Joomla TemplatesBest Web HostingBest Joomla Hosting

Home
Previous Next
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4

አመልድ ኢትዮጵያ በ2015/ 2016 ዓ.ም በአማራ እና በአፋር ክልል 6.5 ቢሊዮን ብር በሚጠጋ በጀት በ134 ወረዳዎች 38 ፕሮጀክቶች እንደሚተገበር ተገለጸ፡፡

     amharic dr

አመልድ ኢትዮጵያ 1976 . ጀምሮ ስር የሰደደውን ድህነት እና ረሃብ ለማስወገድ ስትራቴጅ ነድፎ እየሰራ ይገኛል፡፡ የደርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዓለማየሁ ዋሴ (ፒኤች.) ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ".. 2023 በአማራ ክልል እና በአፋር ክልል በጠቅላላ 38 ፕሮጀክቶች ይተገበራሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ 31 ፕሮጀክቶች ከባለፈው ዓመት የቀጠሉ ሲሆኑ 7 ፕሮጀክቶች ግን በአዲስ የሚከፈቱ ናቸው፡፡ 134 ወረዳዎች በአማራ እና አፋር ክልል ላይ እንሰማራለን፡፡ 71 ወረዳዎች የልማት ስራ እንሰራለን፤ 98 ወረዳዎች ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ስራዎች ይከናወናሉ፡፡ በአጠቃላይ .. 2023 ለማንቀሳቀስ ያሰብነው 6.5 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ በጀት ነው" ብለዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ በጋዜጣዊ መግለጫቸው እስካሁን ለማህበረሰብ ልማት ድጋፍ ያደረጉ ለጋሾችን አመስግነው በቀጣይም ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

"የልማት ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የአካባቢው ህብረተሰብ ከዚህ በፊት እንደሚያደርገው አመልድ ኢትዮጵያ የራሴ ድርጅት ነው የሚሉት፡፡ ንብረቶችን ይጠብቃል፣ አላስፈላጊ ድርጊቶች ሲፈጸሙ ሪፖርት ያደርጋል፣እኛ ምንሰጣቸው ድጋፍ ደግሞ መነሻ እንጅ መጨረሻ እንዳልሆነ ያውቃሉ፤ስለዚህ እኛ በምናደርገው ድጋፍ ተነስተው ወደ ተሻለ ኑሮ እንዲመጡ እስካሁን የሚያደርጉትን ትብብር ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡ በሌላ በኩል በአካባቢው ያሉ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች አመልድ ኢትዮጵያን እንደራሳቸው የበጀት አካል አድርገው ክትትል እንዲያደርጉ በዚህ አጋጣሚ ጥሪየን አቀርባለሁ፡፡ እንደዚሁም ከእኛ ጋር አብረውን የሚሰሩ እምነት የጣሉብን አለም አቀፍ ድርጅቶች እስካሁን ለሰጡን ድጋፍ እና እምነታቸውን በእኛ ላይ ስለጣሉ፣ ወደፊትም አብረውን ስለሚሰሩ እናመሰግናለን" ብለዋል ዋና ዳይሬክተሩ፡፡